Sunday, September 8, 2013

የክርስቲያኖች አኗኗር




                   ክርስቲያኖች ከሌሎች ሰዎች ወይ በሀገር ወይ በቋንቋ ወይ በሚያዩዋቸው ልማዶች አይለያዩም። እነርሱ በራሳቸው ከተሞች አይኖሩምና፤ የተለየ የአነጋገር ስልት አይጠቀሙምና፤ ወጣ ባለ ነገር የሚገለጽ ሕይወትንም አይኖሩምና ፡፡ እነርሱ የሚከተሉት ሥነ ምግባር በማንኛውም ክልስ ሐሳብ ወይ ጣልቃ ገብ ሰዎች የተቀየሰ አይደለም ፤ጥቂቶች እንደሚያደርጉትም የማንኛውም የሰው ልጅ መመሪያ አስፋፊ አድርገው ራሳቸውን አያስተዋውቁም። ነገር ግን በግሪክና በባርባር ከተሞች በመኖር እያንዳንዳቸው በተወሰኑበት መሠረት ከአለባበስ ከምግብ እንዲሁም ከተቀሩት መደበኛ ሥነ ምግባሮች አንጻር የነባር ነዋሪዎችን ልማዶች በመከተል የራሳቸውን አስደናቂና ማራኪ የሆነውን የሕይወት ዘይቤ ይገልጡልናል፡፡
                   እነርሱ በራሳቸው ከተሞች ይኖራሉ ነገር ግን እንደ ተራ መጻተኞች ሆነው ፡፡ እንደ ዜጎች በሁሉም ነገሮች ከሌሎች ጋር ይጋራሉ ቢሆንም እንደ ባዕድ ይቸገራሉ፡፡ማንኛውም ባዕድ መሬት ለእነርሱ እንደ እናት መሬት ነው እንዲሁም ማንኛውም የተወለዱበት መሬታቸው ለእነርሱ እንደ መጻተኞች መሬት ነው፡፡ሌሎች ሁሉ እንደሚያደርጉት እነርሱ ይጋባሉ ልጆችን ይወልዳሉ ዘራቸውን ግን አያጠፉም።የጋራ ጠረጴዛ/ማዕድ አላቸው የጋራ አልጋ/ርኩሰት ግን የላቸውም፡፡እነርሱ በሥጋ ውስጥ ናቸው ነገር ግን ሥጋን እየተከተሉ አይኖሩም። ቀኖቻቸውን በምድር ላይ ያሳልፋሉ ነገር ግን እነርሱ የመንግስተ ሰማያት ዜጎች ናቸው፡፡
                 የተሰጡትን ሕግጋት ይከተላሉ በተመሳሳይ ጊዜም በሕይወታቸው አብልጠው ይከተሏቸዋል፡፡ሁሉንም ሰዎች ይወዳሉ እንዲሁም በሁሉም ይተቻሉ፡፡እነርሱ ያልታወቁና የተወቀሱ ናቸው፤ እነርሱ ለሞት የተሰጡ ናቸው እንዲሁም ለሕይወት የተጠበቁ ናቸው፡፡እነርሱ ድሆች ናቸው ቢሆንም ብዙዎችን ባለጠጎች ያደርጋሉ፤ እነርሱ ሁሉን ያጡ ናቸው ቢሆንም ሁሉም የሞላላቸው ናቸው፤እነርሱ የተዋረዱ ናቸው ቢሆንም አብዝተው በተዋረዱ መጠን የተከበሩ ናቸው፡፡እነርሱ መጥፎ ይነገርባቸዋል ቢሆንም የተመሰከረላቸው ናቸው፡፡እነርሱ የተጠሉና የተባረኩ ናቸው፡፡እነርሱ የተሰደቡና ስድቡን በበጎ የሚመልሱ ናቸው፤እነርሱ ጥሩ ያደርጋሉ ቢሆንም እንደ ክፉ ሰሪ ይቀጣሉ።በተቀጡ ጊዜ ወደ ሕይወት እንደሚፈጥን ሰው ደስ ይላቸዋል፤እነርሱ እንደ ባዕድ በአይሁድ የተጠቁ ናቸው በግሪኮችም የተገፉ ናቸው ቢሆንም እነርሱን የሚጠሉ ለጥላቻቸው ምንም ምክንያት ማቅረብ አይችሉም፡፡
የማቴተስ መልዕክት ወደ ዲዮግናጠስ  /2ኛ መቶ ዓመት

መስቀል፡ የምንቀብረው ወይስ የምንሸከመው?

   ''ከተሰቀለው ከኢየሱስ ጋር እንጂ ከተሰቀለበት መስቀሉ ጋር ምን አለን...'' ለሚሉት ግሩም ምላሽ ይመልከቱ።